“ታላቁ የህዋ ምርምር ማእከል የሆነው ናሳ ትላንት ባሰራጨው አስደንጋጭ ሰበር ዜና የፊታችን ታህሳስ ወር December 2014 አለም ለ 6 ቀናት በድቅድቅ ጨለማ ትዋጣለች አለ::”

Screen-Shot-2014-10-24-at-6_36_06-PM

ቢንያም መንገሻ October 27,2014

ለመላው አለም: ናሳ አስረግጦ በትላንትናው ጋዜጣዊ መግለጫው እንዳስታወቀው ምድራችን ከፊታችን ለሚመጣው ታህሳስ ወር December 2014 ለ 6 ቀናት በታላቅ ድቅድቅ ጨለማ ትዋጣለች::

ይለናል የጠፈር ማእከሉም በማስከተለም ለ6 ቀን በተከታታይ ፀሐይ የምትጨልምባቸውን ቀኖች ይፋ አድርጓል እንደ ናሳ ዘገባ የ6 ቱ ቀን ድቅድቅ የምድራችን ጨለማ የሚጀምረው ከታህሳስ ከእለተ ሀሙስ 16 እስከ ሰኞ ታህሳስ 22 2014 ሲሆን የአለማችን ለ6 ቀናት በድቅድቅ ጨለማ የምትዋጥበት ምክንያት ታላቅ የህዋ አውሎ ንፋስ ፀሐይን ስለሚመታትና ከሌሎች ፕላኔቶች በሚነሳው አዋራ አማካኝነት ፀሐይ በአዋራ ተሸፍናና ተደፍና ስለምትቆይ ነው:: በተጨማሪም በአላማችን ላይ በእነዚያ በ6 ቀናት ውስጥ ታላላቅ ችግሮችና ጥፋቶች ሊከሰቱ ይችላሉ ይለናል የታላቁ የጠፈር ምርምር ማእከል የሆነው የናሳ ባለስልጣን ቻርልስ ቦልደን::

2014-10-26_100458-copy-675x419

About " ማራናታ " !

“የተወደዳችሁ ውድ የዚህ ጦማር ተቋዳሾች በእግዚያብሔር ቸርነት እና ፈቃድ በተከታታይ የማወጣቸውን ጽሁፎች እንድትመገቡልኝና እንድታጣጥሙልኝ በስተመጨረሻም ያጣጣማችሁትን ጣእም ደግሞ እንድታሳውቁኝ በእግዚያብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እጠይቃችኋለው ምክንያቱም ለመውጣትም ሆነ ለመውረድ የእናንተን ጣእም በጣም ወሳኝ ነውና ይህንን መጦመሪያ እንዳዘጋጅ የረዳኝ እግዚያብሔር ነው:: እኔ ብዙ ግዜ እንዲህ በማለት አምን ነበረ ማንኛውም ነገር በሰው ሀይል የተፈለገው ነገር ሁሉ ይገኛል የሚል የጸና እምነት ነበረኝ ለዚህም በፓለቲካዊና በማነቸውም ለለውጥ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ላይ የአቅሜንና ያመንኩበትን ሀሳብ ተሳትፎና ድጋፍ አደርግ ነበረ ነገር ግን ይህ የሚፈለገው ፓለቲካም ሆነ ማንኛውም ለውጥ ግን ከዛሬ ነገ ይሻላል ሲባል የሚፈገለገው ነገር ከመባሱ በስተቀር ጠብ ያለ ነገር የለም ስለዚህም ያልተኬደበትን መንገድ መፈለግ ጀመርኩ መንገዱን የጀመርኩት ከእራሴ በመነሳት ነው እራሴን ጠየቅኩኝ እኔ ማን ነኝ? ወደ እዚህች አሰቃቂ አለም እንዴት መጣሁ? እኔ ፈልጌ ነው ወይስ ቤተሰቦቼ? የት ድረስ ነው አቅሜ? ያለፉት ህይወቶቼ ምን ይመስል ነበር? ከአሁን ቡኋላ እንዴት ነው ሀይወቴን የምገፋው? ሌሎችንም ጥያቄ ይዤ በእምነቴም ክርስቲያንም ስለሆንኩ ወደ አመንኩት አምላክ ወደ እግዚያብሔር ቃል ዞርኩ ሁሉን ወደሚችለውና ወደ ሚያውቀው የእግዚያብሔርን ቃል ማጥናት ስጀምር እያንዳንዷን የዚህችን አለምና ስንክሳርና የሚመጣውን ጭምር የሚናገር መጽሀፍ ሆኖ አገኘሁት መጽሀፍ ቅዱስን በጣም ደግሞ የገረመኝ ሌላው ቢቀር አሁን ያለውን ነባራዊ የአከም ሁኔታ እንኳ ስለግብጽና ስለሶሪያ በደንብ አስረግጦ ይነግረናል:: በአለም ላይ እየተደረጉ ስላሉት ሀይማኖታዊ : ፓለቲካዊ : ኢኮኖሚያዊ : ማህበራዊ ቀውሶችን እና መፍትሄያቸውንም ጭምር ይነግረናል ይህንን ታላቅ መጻፍ ለምን ሰው ዝም ብሎ ተራራ ከሚገፋ እውነቱን አውቆ በቀላሉ ወደ እግዚያብሔር በመዞር ያን ለሰው ተራራ የሆነውን ለእግዚያብሔር ደግሞ አይኑ ወስጥ የማይገባውን ነገር ለእግዚያብሔር አስረክቦ ባሸናፊው አምላክ አያሸንፍም ብዬ አሰብኩና የገባኝን የምድራችን ስንክ ሳር በእግዚያብሔር ቃል መክፈቻ እየከፈትኩ ለወገኖቼ አላቀርብም በማለት በልቤ አሰብኩ እግዚያብሔርም እረድቶኝ ሀሳቤ እውን ሆነ በፌስ ቡክ ላይ በጅማሬ የተጀመረው ይህ ጦማር ዛሬ “ማራናታ” በሚል የመጦመሪያ ስም እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ለእናንተ የንባብ ማእድ በሩ ክፍት አድርጌ እንሆኝ እላለው:: ማሳሰብ የምፈልገው መነገር የምፈልገው የሀይማኖት ስርአት ለማስተማር አስቤ ሳይሆን የአለማችንን ጉድ በሙሉ የያዘውን የእግዚያብሔር ቃል እንድታዩት ለማሰታወስ ነው:: መልካም ማእድ ይሁንላችሁ በማለት ልባዊ እምነቴ ነው::” የእግዚያብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ በነገር ሁሉ ላይ ጌታ ነው:: ! የእግዚያብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ከነገር ሁሉ ያድናል:: ! ማራናታ ! አሜን ! ጌታ ሆይ ቶ ሎ ና ! ቢንያም መንገሻ
This entry was posted in News. Bookmark the permalink.

Leave a comment